በተመሳሳይ የህወሃት ከፍተኛ አመራር የሆኑት በምክትል ከንቲባ ማእረግ የአዲስ አበባ ከተማ የትራንስፖርት ቢሮ ኃላፊው ሰለሞን ኪዳነ (ዶ/ር) ከስልጣን እንደሚነሱ ደብዳቤ እንደደረሳቸው ለቢቢሲ አረጋግጠዋል። ይህን ተከትሎ ህወሃት ባወጣው መግለጫ አባላቱን ከፌደራል ከፍተኛ የሃላፊነት ደረጃዎች እንዲሁም ከአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የማንሳት እርምጃ ህግን የጣሰና ችግርም የሚያስከትል ነው ብሏል።
ብልፅግና ፓርቲ በበኩሉ የተደረገው የተለመደ ሹም ሽር ስለሆነ ከብሄር እና ከፖለቲካ ጋር ማገናኘት አይገባም ሲል ምላሽ ሰጥቷል።